
የሰው ተፈጥሮ
ሰው ማዝራቱ አይታየውም አሉ አበው ሲተርቱ ፡፡ አዋ የራሳችንን ጉደረለት ከማየትና ከመረም ይልቅ በሌሎች ስህተት መሳቅና መሳለቅ ይቀናናል፡፡ የሌሎች መሳሳት የኛን ትልቅነት የሚያጎላው እየመሰለን ይሆን?ብቻ ስለ ሰዋች ደካማነት ካላወራንም ጨዋታም የማይደምቅ የማይመስለን አለን፡፡ አበውስ ሰው ካላማ ዥንበር አያጠልቅም ብለው የለ፡፡ በአንድ ወቅት ማዳም ዶ ፎንቴን .. ስለራሳቸው መልካምነትና ከፍተኛነት ስለሌሎች አጉልነትና ዝቅተኛነት አንዳይናገሩ ቢከለክሉ ስንት ሰዋች ዲዳ በሆኑ ነበር፡፡ .. ብላ ጽፋለች ፡፡ በተለይ ወሬ እንደ ባህል እየተለመደ የመጣበት አካባቢ ይህ ቢሆን የዲዳዋች ከተማ ተንሰራፋ ማለት ይቻል ይሆናል፡፡
አንድ ሰው በማህበረሰቡ ተቀባይነት እንዲኖረው በማህበራዊ ኑሮው አቀራረቡ ሰብዕናው እንዲለይ የግድ ስለሌሎች መጥፎነት መናገር ወይም ደግሞ መረን የለቀቀ /በማንኛውም ረገድ/ ዝላይ ማብዛት አይኖርበትም ፡፡
የኦስትሪያው ስነ ልቡና ተመራማሪ አልፎሬድ አድለር ስለሰብዕና ባለው ንድፈ ሃሳብ የሰው ልጅ ለሥልጣን /የበላይነት ስላው ከፍተኛ ፍላጎትና በጭፍን ከሚሰሩ ይልቅ በማወቅ በሚሰሩ እንቅስቃሴዋች አስፈላጊነት ላይ ትኩረት በመሰጠቱ ይታወቃል ፡፡
ፍሮይድ ታላቁ የስነልቡና ጠቢብ ሰብዕናን ደመ ነፍስ የግል ህይወት ልምድና ለህሊናና ግብረገብ የሚገዛ አስተሳሰብ / በማለት የሶስት ደረጃዋች ውጤት አድርጎ ያስቀምጠዋል ፡፡
ደመ ነፍስ / / መደሰቻ መርሆ / / የሚባለው ሲሆን ህጻን ልጅ ሲርበው የሚጮሀው ጩሀት ዓይነት ነው፡፡ ይሀውም ሲረበው የሚሰማውን መትፎ የረሃብ ስሜት በጣም በማልቀስ እንዲተወው ለማድረግ የሚፈጥረውነው፡፡
የግል ህይወት ልምድ/ / የእውነታ መርሆ / / ሲሆን አንድ ህጻን ልጅ እሳት የሚፋጅ መሆኑን ለይቶ ከእሳቱ ለመሸሳ በሚወስደው ጥንቃቄ ይገለጻል ፡፡
የሚቀትለው ደረጃ ለህሊናና ግብረ ገብ የሚገዛ አስተሳሰብ ሲሆን ይሄ ደግሞ በማህበራዊ ኑሮ ውስጥ ሊያውቃቸው የሚገበቡት ደንቦች የሚያውቅበት ነው፡፡ ለምሳሌ የማዕድ ስነ ሳርዓትና የመሳሰሉትን፡፡
ከነዚህ ደረጃዋች እንግዲህ ሰብእናን እናገኛለን ፡፡ የሰብዕናው መማላትና አለመማላት ትክክለኛ መሆንና አለመሆን ግን አንድ ሰው ከሚያድግበት ቤተሰብ ት/ ቤትና አካባቢው ጋር በተያያዘ ሁኔታ የወሰናል፡ ቻ
አንድ ህጻን ሁሉንም ያገኘውን ነገር ወደ አፉ የሚከትበት ደረጃ ላይ እያለ አሳዳጊዋቹ መጫወቻዋቹን በንጽህ ሁኔታ አጥቦ በማቅረብ ፋንታ አፉ ውስጥ እንዳይከታቸው ቢቆጡና ዕቃዋቹን ቢያርቁበት በሚያደርገው ትግል በማበረታታት ፋንታ ቁጣና ቁንጥጫ የሚሰጡ ከሆነም ወደፊት በሚኖረው ስብዕና ላይ ተጽዕኖ አድርገዋል ፡፡ ያንን ዕንቡጥ ፍሬ ግን ብዙ በጣም ብዙ ጥሩ ነገሮች ሊያደርጉለት በተገባ ነበር ፡፡
እነዚህ ሁኔታዋች ሁሉ በሰብዕና ላይ ከፍተኛ ድርሻ አላቸው፡፡ በአካባቢ ልዪነት የባህል የአናናር የአስተዳደግ እና ሌላም ልዩነት ሰብዕናችን የተለያየ ይሆናል ፡፡
ሰው ሩህሩህ ጎነዝ የዋህ ብልጥ ጨዋ ንቁ ታማኝ ቁም ነገረኛ ለጋስ ክፉ ምቀኛ እብሪተኛ ሴሰኛ ስስታም ………… ወዘተርፈ .. ነው ፡፡ የሆነው ቢሆን ግን ይፈልጉት ሳይሆን ከማህበረሰቡ የተማረው ነው፡፡ ማህበረሰቡ በጥሩ ሁኔታ ኮትኩቶ ያሳደረገው ካልሆነ ከሱ ጥሩ ነገር ሊጠበቀወ አይችልም ፡፡
ትንሽ ቆየት ቢልም ከአንዲት ልጅ ማስታወሻ ላይ ያገኘኃቸው ትያቄዋች እነዲህ ይነበባሉ ፡፤ ሰው ምንስ ትልቅና ትንሽ ነገር ነው በቀን ስንት ጊዜ አጥፍቶ ስንት ጊዜስ ያልማል ምን ያህል ከፍተኛና ምን ያህል ዝቅተኛ መንፈስ አለው ምን ያህል አፍቅፎ ምን ያህል ይጠላል ምን ያህል ሩህሩህና ምን ያህል ጨካኝ ክቡርና ምን ያህል ትክክለኛና ምን ያህልስ ስህተተኛ ነው ምን ያህል ክቡርና ምን ያህል ወራዳ ነው ምንያህል ጨዋና ምን ያል ልክስክስ ነው አልፎ አልፎ እነዚህን የመሳሰሉ ጥያቄዋች በመጠኑም ቢሆን በህይወት ላይ ሳይጠቀሙን አይቀሩም ፡፡ ለነገሩ ግን እያንዳንዳችን ምን ያህል ጥሩ ነን
ስለ ሰው ተፈጥሮ ብዙም መጠየቁ ባይከፋማ ካሁን በፊት ምንጩን / ትክክለኛውን / ባላውቅውም የስነልቡና አዋቂዋች እንዲህ ሲሉ ጽፈዋል ፡፡
.. ሰው ወደዚህ ዓለም ሳያስብ ወጥቶ ከፍላጎቱ ውጪ ለቆት ይሄዳል ፡፡ በምድር ላይ በትክክል አይዳኝም ሃሳቡንም የሚረዳው ማንም የለም ፡፡ በሕጻንነቱም መልእክ በወጣትነቱ ሰይጣን ሙሉ ሰው ሲሆን ደግሞ ጅል ነው ፡፡
ሚስትና ቤተስብ ካለው ደስተኛ ነው፡፡ላጤ ከሂነ ኢሰብአዊና የማይታመን የህዝብ መዝናኛ ቦታ ከገባ ሰካራም ካልገባ ደግሞ ስስታም ነው ፡፡ ድሃ ከሆነ ጭንቅላት የለውም ሃብታም ከሆነ በዓለም ላይ ያለ ዕድል ሁሉ ለሱ ሲሆን እሱ ግን ክፉ ነው፡፡ አእምሮ ያለው ከሆነ ብልጣ ብልጥ እንደሆነ ተደርጎ ይወሰዳል ፡፡ ወደ ቤተክርስቲያን ከሄደ ዲያቆን ነው ካልሄደ ደግሞ ኃትያተኛ ይባላል፡፡ ከመጸወተ ወይ ጥሩ ነገር ከሰራ ራሱን ለመስታወቅ ይህን ካላደረገ ደግጀሞ ገብጋባ ነው፡፡ ወደዚህ ዓለም ሲመጣ/ ሲወለድ /ሁለሉም ሲስመው ይፈልጋል፡፡ የሕወቱ መጨረሻ ሲቃረብ ደግሞ እያንዳንድ ሊመታው ይከጅላል ፡፡ ወጣት ሆኖ ሕይወቱ ካለፈ የወደፊት ሕይወቱ ብሩህ ነበር ይባልለታ፡፡ እስሽምግልናው ከኖረ ሁሉም ሰው የውርስ ኑዛዜ እንዳደረገ ያምናል፡፡ ስለዚህ ሁሉንም ሰው ማስደሰት አይቻልህም ግዳጅህን ተወጣ ፍርሐት አይደርብህ ያለህን የማስተዋል ችሎታ ተጠቀም ፡፡ ስህተት የሰራህ ከሆነ ምንም ነገር ካለመስራት ይሻላል ፡፡
ማንም ሰው ስላንተ ችግር መስማት የሚፈልግ ስለሌለና /አለመኖሩም ጥሩ ነው፡፡ / ቢኖርም ስላንተ ችግር ምንም ማድረግ ስለማይፈልግ ችግርህን ለራስህ ይዘህ ፈገግታ አይለይህ ፡፡ ..እናንተስ ምን አላችሁ?